አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በደቡብ ክልል በጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 4 ሚሊየን ብር የሚገመት የገንዘብ እና የአይነት ድጋፍ አበረከተ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የገንዘብ እና 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የአይነት በጠቅላላው የ4 ሚሊየን ብር ድጋፍ ለክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ አስረክበዋል፡፡