የሀገር ውስጥ ዜና

መንግስት ፕሬዚዳንት ትራምፕ በህዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አስተያየት ማብራሪያ ጠየቀ

By Meseret Demissu

October 24, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 14 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሬይነርን በጽህፈት ቤታቸው አስጠርተው ማብራሪያ ጠይቀዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምባሳደር ማይክ ሬይነርን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው አስጠርተው ፕሬዚዳንት ትራምፕ በህዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አስተያየት ዙሪያ ነው ማብራሪያ የጠየቁት።