አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 14 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህዳሴው ግድብ ሙሌት ዙሪያ ኢትዮጵያ ግብፅና ሱዳን በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር በደቡብ አፍሪካ አማካኝነት እያደረጉ ያሉትን ድርድር የአውሮፓ ህብረት እንደሚደግፍ ገለጸ።
ህብረቱ በመግለጫው ሶስቱ ሀገራት በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት ለችግራቸው ዕልባት ለመስጠት እየሄዱበት ያለውን መንገድ የምንደግፍበት እንጂ አላስፈላጊ ውጥረት የምንፈጥርበት ጊዜ አይደለም ብሏል።