አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኢንጅነር ታከለ ኡማ ከአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ጋር በመሆን የፖታሽ፣ ጨውና ብሮሚን ምርቶች ላይ እየተከናወኑ ያሉ የማዕድን ልማቶችን እየጎበኙ ነው።
ሚኒስትሩ አፍዴራ አካባቢ “ታናራሙ ኬሚካልስ” በተባለ የቻይና ኩባንያ በ57 ሚሊየን ዶላር ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የብሮሚን ፋብሪካን ጎብኝተዋል፡፡