የሀገር ውስጥ ዜና

በሀዋሳ አሮጌ ገበያ የተነሳው የእሳት አደጋ በአንድ ሼድ ውስጥ የነበረ ሸቀጥን አወደመ

By Feven Bishaw

October 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀዋሳ ከተማ አሮጌ ገበያ በተነሳ የእሳት አደጋ በአንድ ሼድ ውስጥ የነበረ ሸቀጥ ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተገለፀ።

የእሳት አደጋው ሌሊት 7 ሰዓት አካባቢ ባልታወቀ ምክንያት የተነሳ ሲሆን ÷በህብረተሰቡ እንዲሁም በፀጥታ ሀይሉ ርብርብ ቃጠሎውን መቆጣጠር እንደተቻለና ወደ ሌላ ሼድ እንዳይዛመት ማድረግ መቻሉ ተነግሯል፡፡