አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 በማህበር የተደራጁ ወጣቶችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡
ምክትል ከንቲባዋ ከብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለስ ዓለሙ እና ከቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን አምባዬ ጋር በመሆን በቦሌ ክፍለ ከተማ በወረዳ 9 ወጣቶች በጥቃቅን እና አነስተኛ ተደራጅተው የሚያደርጉትን የስራ እንቅስቃሴ ነው የጎበኙት፡፡