የሀገር ውስጥ ዜና

ወጣቱ በመደራጀትና የአካባቢውን ፀጋ በመጠቀም ስራ ሳይንቅ ከሰራ የለውጡ ባለቤትና ተጠቃሚ መሆን ይችላል – ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

By Feven Bishaw

October 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 በማህበር የተደራጁ ወጣቶችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡

ምክትል ከንቲባዋ ከብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መለስ ዓለሙ እና ከቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን አምባዬ ጋር በመሆን በቦሌ ክፍለ ከተማ በወረዳ 9 ወጣቶች በጥቃቅን እና አነስተኛ ተደራጅተው የሚያደርጉትን የስራ እንቅስቃሴ ነው የጎበኙት፡፡