የሀገር ውስጥ ዜና

የጤና ሚኒስቴር የጡት ካንሰር ህክምና በ12 ሆስፒታሎች እየተሰጠ መሆኑን ገለጸ

By Abrham Fekede

October 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 12 ሆስፒታሎች የጡት ካንሰር ህክምና እየሰጡ እንደሚገኙ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረው የጡት ካንሰርን ወር በማስመልከት የጤና ሚኒስቴር ጡትዎን በእጅ በመዳሰስ እና በመመርመር የጡት ካንሰርን ይከላከሉ በሚል መሪ ቃል ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል፡፡