የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮች የጥፋት ኃይሎች ባደረሱት ጥቃት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ

By Abrham Fekede

November 02, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮች በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቀናቲ ቀበሌ የጥፋት ኃይሎች ባደረሱት ጥቃት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገለጹ፡፡

አመራሮቹ ድርጊቱን በማውገዝ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በአፋጣኝ ተይዘው ለህግ እንዲቀርቡ ለማድረግ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል፡፡