የሀገር ውስጥ ዜና

የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ወረራ እና ህገ ወጥ ግንባታን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ነው

By Abrham Fekede

November 08, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ወረራ እና ህገ ወጥ ግንባታን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል።

በውይይቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤን ጨምሮ በመሬት፣ በፀጥታ እና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ የሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።