አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2012(ኤፍቢሲ) የብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ከሀገሪቱ የፀጥታና የመረጃ ተቋማት ለተወጣጡ 532 የፀረ-ሽብር ግብር ሃይል ባለሙያዎች ሽብርተኝነትን የመከላከል እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ሥልጠና መሥጠቱን አስታውቋል።
አገልግሎቱ ከመከላከያ፣ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና ከብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ለተወጣጡ የፀረ-ሽብር ግብር ሃይል ባለሙያዎች ነው ስልጠና የሰጠው፡፡