የሀገር ውስጥ ዜና

ነባሩ ሥርዓተ ትምህርት በ2017 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ በአዲስ ሥርዓተ-ትምህርት እንደሚተካ ተገለጸ

By Tibebu Kebede

January 02, 2020

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) ነባሩ ሥርዓተ – ትምህርት በ2017 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ በአዲስ ሥርዓተ -ትምህርት እንደሚተካ ተገለጸ።

በትምህርት ሚኒስቴር የሥርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እሼቱ አስፋው እንደገለጹት፥ አሁን በስራ ላይ የሚገኘውን ስርዓተ – ትምህርት ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በአዲስ ለመተካት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።