የሀገር ውስጥ ዜና

በሀሳብ መሸነፍን በሰላማዊ መንገድ መቀበል የስልጣኔ መገለጫ ነው-የኃይማኖት መሪዎች

By Tibebu Kebede

January 02, 2020

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀሳብ መሸናነፍን በሰላማዊ መንገድ መቀበል የስልጣኔ መገለጫ መሆኑን የኃይማኖት መሪዎች ተናገሩ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ-ክርስቲያናት ህብረት መሪዎች በወቅታዊ የሀገሪቷ የሰላም ሁኔታ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።