አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተከስቶ በነበረው ግጭት እጃቸው አለበት ተብለው በተለዩ ከ450 በላይ በሚሆኑ ተማሪዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ፡፡
በኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተከስቶ የነበረውን ግጭት እና ሁከት አስመልክቶ የሳይንስ እና ከፍተኛ የትምህር ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመሆን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡