አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በኢትዮጵያ የስዊድን አምባሳደር ሀንስ ሄኒሪክ ላንድኩስት እና የዩኒሴፍ ተወካይ አዴሌ ክሆድር የመተከል ተፈናቃዮችን ጎበኙ፡፡
በኢትዮጵያ የሲዊዲን አምባሳደር ሀንስ ሄኒሪክ ላንድኩስት እና የዩኒሴፍ ተወካይ አዴሌ ክሆድር ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የተፈናቀሉ እና በአማራ ክልል ቻግኒ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ጎብኝተዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የሕፃናት ፈንድ (ዩኒሴፍ) ከኢትዮጵያ መንግስትና ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በመሆን ለተፈናቃዮች የጤና አገልግሎት፣ አልሚ ምግብ፣ የውሃና የንጽሕና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ከዩኒሴፍ ኢትዮጵያ የትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!