የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ “ቆሜ ልመርቅሽ” በሚል በሸገር ወዳጅነት ፓርክ ጥላሁንን የሚዘክር ኮንሰርት ላዘጋጁ አካላት ምስጋና አቀረቡ

By Abrham Fekede

March 04, 2021

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “ቆሜ ልመርቅሽ” በሚል በሸገር ወዳጅነት ፓርክ የሚደረገው ዝክረ ጥላሁን ኮንሰርት ላዘጋጁ አካላት ምስጋና አቀረቡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገጻቸው የዝክረ ጥላሁን ገሠሠን ዝግጅት በማስተባበር፣ የተገኘው ገቢ ለ’ገበታ ለሀገር’ እንዲውል ያደረጋችሁ ሁሉ ምስጋናዬ እና አድናቆቴ ይድረሳችሁ ብለዋል።

በተጨማሪም ለተሰበሰበው ከ80 ሚሊየን የሚበልጥ ገንዘብ መዋጮ ያደረጋችሁ ሁሉ የማይደበዝዝ አሻራችሁን በኢትዮጵያ ልማት ላይ አሳርፋችኋል ሲሉ አስፍረዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!