የሀገር ውስጥ ዜና

ተጨማሪ 300 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረብያ ተመለሱ

By Tibebu Kebede

March 10, 2021

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት ተጨማሪ 300 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረብያ ጂዳ ከተማ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል አድርገዉላቸዋል።

መንግስት ከሳዑዲ አረቢያ እና ከሌሎች ሀገራት በችግር ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን እየመለሰ ይገኛል።

በዚህም በቅርብ ጊዜያት ከሳዑዲ እና ሊባኖስ በሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው የሚታወስ ነው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!