የሀገር ውስጥ ዜና

ዩ ኤስ ኤይድ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ የሚገመት የሕክምና ቁሳቁሶችን ለትግራይ ክልል ድጋፍ አደረገ

By Tibebu Kebede

May 14, 2021

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ከ800 ሺህ ዶላር በላይ የሚገመት የሕክምና ቁሳቁሶችን ለትግራይ ክልል እንዲደርስ ለኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅርቦት ኤጀንሲ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል፡፡

ድጋፉ በትግራይ ክልል ለሚገኙ 40 የጤና ተቋማትና ለሰባት የወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ደርሷል ተብሏል፡፡

ድጋፍ የተደረጉ ቁሳቁሶችን በማድረስ ለተሳተፉ አካላት ድርጅቱ ምስጋና ማቅረቡን ከድርጅቱ የትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!