አዲስ አበባ፣ ጥር 18 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር በማጠናከር የመከላከያ ኃይሏን ማዘመኗን መቀጠል እንደምትፈልግ በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ ገለፁ።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር ያላትን ትብብር በማጠናከር የመከላከያ ሰራዊቷን በተለይ ሰላም በማስከበር እና ሽብርን በመከላከል ተግባር ላይ ጦሯን ማዘመን እንደምትፈልግ ተናግረዋል።