የሀገር ውስጥ ዜና

አዲስ ወግ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው

By Feven Bishaw

July 27, 2021

ዶ/ር ንጉሡ አክሊሉ የምርጫ ቦርድ፣ የመንግሥት አካላት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙሀን፣ የሲቪክ ማኅበረሰብ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት በምርጫው ሂደት የተጓዙበት መንገድ ተስፋን የሚፈነጥቅ ነው ብለዋል።

የፍትሕ አካላት፣ የጸጥታ አካላትና የመገናኛ ብዙሀን ገለልተኝነት ከምንጊዜውም የተሻለ መሆኑንም አንስተው የፖለቲካ ፓርቲዎች ለሕዝብ ክፍት ሆኖም ዝግ ሆኖም ምክክርና ውይይት ማካሄዳቸው ሂደቱ የተሳለጠ እንዲሆን አስችሏል ነው ያሉት።

አቶ ሲሳይ ቶላ በበኩላቸው ምርጫውን የማስፈጸም ሂደቱ ዋነኛ ኃላፊነት የምርጫ ቦርድ ሲሆን፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ሰላማዊ እንዲሆን መንግሥት የአጋዥነት ሚናን ተጫውቷል።

ከ37 ነጥብ 4 ሚሊየን የሚበልጥ ሕዝብ ለምርጫ ተመዝግቦ ከ49 ሺህ በሚበልጡ የምርጫ ጣቢያዎች በከፍተኛ ፍላጎት የተሳተፈበት ነበር ነው ያሉት።

በቅድመ ምርጫም ልዩ ልዩ አስቻይ ማዕቀፎች ወጥተዋል፤ ምርጫ ቦርድን ያካተተ እና ከልዩ ልዩ የመንግሥት የጸጥታ እና ደህንነት አካላት የተውጣጣ ኮሚቴ ተዋቅሯል ነው ያሉት።

አቶ ሰይፈ ደርቤ ሁሉም የመገናኛ ብዙሀን ተቋማት ወገንተኝነታቸውን ለሙያቸው አድርገው ፓርቲ ሳይሆን ሀገር ታሸንፍ በሚል መርህ በገለልተኝነት ሠርተዋል ነው ያሉት።

የልዩ ልዩ ኃይሎችን ሀገር አፍራሽ ወሬ፣ ምርጫውን አስመልክቶ ስጋት ለመፍጠር የተደረጉ ሙከራዎችን በማምከን በምርጫው ሂደትና በአስፈጻሚ አካላት አመኔታ አድሮበት ሕዝቡ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲሳተፍ አግዘዋል ብለዋል።

የምርጫው ዕለትም ልዩ ልዩ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁመው ከጅማሬ እስከ ፍጻሜው በትጋት ዘግበዋል።