የሀገር ውስጥ ዜና

መኢአድ የክተት ጥሪውን እንደሚቀላቀል አስታወቀ

By Tibebu Kebede

July 28, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የአማራ ክልል መንግሥት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ እንደሚቀላቀል አስታወቀ፡፡

ፓርቲው ጥሪው ሀገር ለማዳን የቀረበ ብቸኛ አማራጭ በመሆኑ ጥሪውን በመቀበል እንደሚቀላቀል መግለጹን አሚኮ ዘግቧል።

መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት በየደረጃው የሚገኙ አባላቱና ደጋፊዎቹ ሀገራዊ ጥሪውን እንዲቀላቀሉ ጠይቋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!