አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮና ቫይረስ በመያዝ የተጠረጠሩ አራት ኢትዮጵያውያን በሀገር ውስጥ ምርመራ ነፃ መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን ለተጨማሪ ምርመራ ናሙናቸው ወደ ደቡብ አፍሪካ መላኩ ተገለፀ።
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዛሬ በሰጡት መግለጫ እነዚህ ከቻይና ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ የነበሩ አራት ኢትዮጵያውያን የሰውነታቸው የሙቀት መጠን ከፍ በማለቱ በጥርጣሬ በኳረንቲን ተለይተው ህክምናቸውን እየተከታተሉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።