አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 23፣ 2013 ( ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከተባበሩት መንግስታት የፖለቲካና ሰላም ግንባታ ጉዳዮች ዋና ፀሀፊ ዶክተር ሮዝማሪ ዲካርሎ ጋር ተወያዩ፡፡
ሚኒስትሯ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ በውይይቱ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች በተለይም በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ከአንድ ወገን የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ ስላለው የሰብዓዊ እርዳታ አስመልክቶ በስፋት መክረዋል።