የሀገር ውስጥ ዜና

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የ2014 ዓ.ም ረቂቅ በጀት 2 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ እንዲሆን ወሰነ

By Melaku Gedif

July 30, 2021

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀረሪ ክልላዊ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት የ2014 ዓ.ም የክልሉ መንግስት ረቂቅ በጀት 2 ቢሊየን 983 ሚሊየን 703 ሺህ 873 ብር እንዲሆን ውሳኔ አሳልፏል፡፡

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) ለሁለት ቀናት ሲያካሄድ የነበረው ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ አጠናቋል።