የሀገር ውስጥ ዜና

የሲዳማ ክልል ለመከላከያ ሰራዊት የ45 ሚሊየን ብር የአይነትና የገንዘብ ብር ድጋፍ አደረገ

By Melaku Gedif

July 31, 2021

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ብሐራዊ ክልላዊ መንግስት ለመከላከያ ሰራዊት የ45 ሚሊየን ብር የአይነት እና የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡

በመከላከያ ሚኒስቴር የሕብረት ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ የፋይናንስ ስራ አመራር ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጄነራል አስረስ አያሌው÷ ክልሉ የሽብር ቡድኑን ህወሓት ለማስወገድ እየተፋለመ ለሚገኘው መከላከያ ሰራዊት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡