የሀገር ውስጥ ዜና

በሶማሌ ክልል ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ሲያዘዋውሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

By Tibebu Kebede

January 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሶማሌ ክልል ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ሲያዘዋውሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ከጅግጅጋ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው መጋሎቀረን መቆጣጠሪያ ጣቢያ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ በቶጎጫሌ ድንበር በህገወጥ መንገድ በአንድ ተሽከርካሪ ተደብቆ ሊገባ የነበረ 39 ሽጉጥ ከተጠርጣሪዎቹ ጋር መያዙ ተጠቁሟል።