የሀገር ውስጥ ዜና

በ2014 በጀት ዓመት ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር ከ1 ቢሊየን ብር በላይ በጀት ተይዟል

By Feven Bishaw

August 09, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በ2014 በጀት ዓመት ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር 1 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በጀት መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተማሪዎች ምግብ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

የኤጀንሲው ዳይሬክተር አቶ ኢሳያስ ምህረት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት÷ በጀቱ ከአምናው ጋር ሲነፃፀር የ500 ሚሊየን ብር ብልጫ አለው፡፡