የሀገር ውስጥ ዜና

የሐረሪ ክልል ምከር ቤት ከ2 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

By Melaku Gedif

August 21, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሐረሪ ክልል ምከር ቤት ለ2014 የስራ ዘመን ማስፈጸሚያ የሚውል ከ2 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጸደቀ።

ምክር ቤቱ እያካሄደ ባለው ስድስተኛ ዓመት አንደኛ መደበኛ ጉባዔ የበጀት እቅዱን ያቀረቡት የክልሉ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልሃኪም አብዲ ናቸው።