የሀገር ውስጥ ዜና

የድሬደዋ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ከመከላከያ ሰራዊት ጎን እንደሚቆሙ ገለጹ

By Melaku Gedif

August 21, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የድሬደዋ አስተዳደር ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ለመስጠት ኪነ ጥበብ ለሀገራዊ አንድነትበሚል መሪ ቃል የኪነ ጥበብ መድረክ በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡

በመድረኩ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ፣ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ በየደረጃው ያሉ የጸጥታ አካላት እና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።