የሀገር ውስጥ ዜና

ሽብርተኛው ህውሓት የፈጸመውን ግፍ የሚያወግዝ ሰልፍ በዲግ ዲጋ ተካሄደ

By ዮሐንስ ደርበው

August 22, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋሊ ኮማ ቀበሌ በንጹሀን ዜጎች ላይ በሽብርተኛው የህወሓት ቡድን የተፈጸመውን ጭፍጨፋ የሚያወግዝ ሰልፍ በዲግ ዲጋ ተካሄደ።

በአፋር ክልል ፊንቲ ረሱ ዞን ዲግ ዲጋ ቀበሌ በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በሽብርተኛው ቡድን ጥቃት የቤተሰብ አባሎቻቸውን ያጡ የጥቃቱ ሰለባዎች ተሳትፈዋል።