የሀገር ውስጥ ዜና

የኮሮና ቫይረስን ለመከላከልና የለይቶ ማከሚያ የህክምና ማዕከላት የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጎበኘ

By Tibebu Kebede

January 31, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኖቭል ኮሮና ቫይረስ አስቀድሞ መከላከል እና የለይቶ ማከሚያ የህክምና ማዕከላት ላይ እየተሰራ ያለው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ጉብኝት ተካሄደ።

የጤና ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮች እና የሲዲሲ ተወካዮች የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ተዘዋውረው መጎብኘታቸውን የጤና ሚኒስቴር ያወጣው መረጃ ያመለክታል።