አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ከአዲስ አበባ መስተዳድር ጤና ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ዮሃንስ ጫላ ጋር በየካና ካዛንቺስ ጤና ጣቢያዎች ያለውን የኮቪድ-19 ክትባት አገልግሎት አሰጣጥን ጎበኙ፡፡
ሚኒስትሯ በጉብኝቱ ህብረተሰቡ የክትባት አገልግሎቱ ለማግኘት በጤና ጣቢያዎቹ በመምጣት እየወሰደ መሆኑን ለማየት ችለናል ያሉ ሲሆን ÷ከክትባት አገልግሎቱ በተጨማሪም ፈጣን የኮቪድ ምርመራ ለህብረተሰቡ እየተሰጠ መሆኑ የሚበረታታ ነው ብለዋል።