አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)ተከማችቶ የቆየውን ሕገወጥ እና የሌብነት ተግባር ለማጥፋት በተደራጁ ሌቦች ላይ ተገቢው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል፡፡
ሆኖም ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከነዋሪው ጋር ተቀናጅቶ መሥራት እና እነዚህ ህገወጥ ተግባር ፈጻሚ ሌቦችን የሚያጋልጥ የከተማው ነዋሪ ሊያበረታታ የሚያስችል የማበረታቻ ሥርዓት በመዘርጋት ሕገወጥነትን መከላከል አስፈላጊ በመሆኑ የከተማው ካቢኔ ባሳለፈው ውሳኔ “ሕገ-ወጥነትን ለሚጠቁሙ መረጃ አቅራቢዎች ስለሚሰጥ ማበረታቻ ደንብ” አውጥቷል፡፡