አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ማዕከል የሚኒስትሮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል፡፡
በውይይቱ በአፋር እና አማራ ክልልሎች የሰብዓዊ ድጋፍ ክንውን ያለበት ደረጃ፣ የሴክተር መስሪያ ቤቶች ክንውን፣ ልዩ ትኩረት የሚሹ አካባቢዎች ላይ የተለየ ትኩረት በመስጠት ድጋፍ የሚከናወንበት አግባብ፣ በሂደቱ ያሉ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ያሉበት ደረጃ፣ እንዲሁም በአጠቃላይ የመልሶ ማቋቋም እቅድ ዝግጅት መጀመር እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡