የሀገር ውስጥ ዜና

ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች የአስተዳደር ቢዝነስ ልማትና የአይሲቲ ፎረም ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል

By Melaku Gedif

September 01, 2021

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢሲ) ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች የአስተዳደር ቢዝነስ ልማትና የአይሲቲ ፎረም በድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል፡፡

ከ40 የሚበልጡ ዩኒቨርሲቲዎች በሚሳተፉበት በዚህ ፎረም ላይ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በመረጃ ደህንነትና በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ ውይይት ይደረጋል ተብሏል።