አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በጎንደር ከተማ የሚኖሩ ባለሀብቶች፣ ነጋዴዎችና የሲቪክ ማህበራት ማይጠብሪ ግንባር ለተሰለፈው ሠራዊት ግንባር ድረስ በመገኘት የተለያዩ ድጋፎችን አድርገዋል።
የድጋፉ አስተባባሪ አቶ ሙሉቀን ሲሳይ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት÷ የተሰጠው ድጋፍ 11 ሺህ አልባሳት ፣ ምግብ፣ 4 ኩንታል ቴምር፣ 600 ካርቶን ብስኩትና 500 ደርዘን ውሃ ሲሆን÷ ወደፊትም ድጋፉ ይቀጥላል ብለዋል።