የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ልማት ዘርፍ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል

By Feven Bishaw

September 06, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ልማት ዘርፉ የኮሮና ቫይረስ ፣ የጸጥታ እና የፖለቲካ አለመረጋጋት ውስጥ ሆኖ በርካታ ተግባራት መከናወናቸው ተገለፀ፡፡

በዚህም የፖሊሲ ለውጦችን በማድረግ የቅድመ አንደኛ ደረጃ በሁለት ዓመት እንዲጠናቀቅ፣ መካከለኛ ደረጃ ከ 7ኛ እስከ 8ኛ ክፍል እና ሁለተኛ ደረጃ ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል እንዲሆን መደረጉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡