የሀገር ውስጥ ዜና

አዲሱ ዓመት ካጋጠሙን ፈተናዎች ወጥተን ስኬት ለማስመዝገብ በትኩረት የምንሠራበት ነው- አቶ አሻድሊ ሀሰን

By Feven Bishaw

September 10, 2021

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)አዲሱ ዓመት ከዚህ ቀደም ካጋጠሙን ፈተናዎች ወጥተን ስኬት ለማስመዝገብ በተለየ ትኩረት የምንሠራበት ነው ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልለ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ፡፡

የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር የ2014 ዓ.ም አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ለመላው የክልሉና የኢትዮጵያ ሕዝብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡