የሀገር ውስጥ ዜና

ምክትል ጠ/ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ ከሰሜን ወሎ ግምባር ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

September 16, 2021

አዲስ አበባ ፣መስከረም 6፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ መከላከያ ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ በሰሜን ወሎ ግምባር ተገኝተው ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በግዳጅ አፈፃፀም ዙሪያ ተወያዩ።

በግምባሩ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ለምንም የማይበገረው የመከላከያ ሠራዊቱ ከቀደምት የኢትዮጵያ ታሪክ በመነሳት በሀገሪቱ ህልውና ላይ የተጋረጠውን አሸባሪ ሀይል ለመደምሰስ እያደረገ ያለውን ስኬታማ ኦፕሬሽን አድንቀዋል።