የሀገር ውስጥ ዜና

የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶችን ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ለማዋል እየተሰራ ነው

By Feven Bishaw

September 23, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ማህበረሰቡ ወደተለያዩ ተቋማት በአካል በመሄድ የሚያገኛቸውን አገልግሎቶች በኤሌክትሮኒክ ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው አገልግሎቶችን እንዲያገኙ እያደረገ መሆኑን ገለፀ፡፡

ከአዲስ አበባ 121 ወረዳዎች ለተውጣጡ ወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል፡፡