የሀገር ውስጥ ዜና

የምዕራብ ጎጃም ዞን ለጸጥታ ሃይሎች ከ4 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የዓይነት ድጋፍ አደረገ

By Meseret Awoke

September 23, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የምዕራብ ጎጃም ዞን በማይጠብሪ ግንባር ህወሓትን እየተፋለመ ለሚገኘው መከላከያ ሰራዊት፣ ለክልል ልዩ ሃይሎች፣ ሚሊሻ እና ፋኖ 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የዓይነት ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉን የምዕራብ ጎጃም ዞን የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ይሁኔ ስጋት ለሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር አቶ ያለአለም ፈንታሁን አስረክበዋል።

ድጋፉ 342 በግ እና ፍየል፣ 14 ሰንጋዎች እና 708 ኩንታል የምግብ እህል መሆኑ ተገልጿል።

ዞኑ በቀጣይም ለመከላከያ ሰራዊት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ይሁኔ ተናግረዋል።

በመላኩ ገድፍ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!