አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ገመዳ ዋይሶ፣ ሰንበቴና አሚና የሰው ሰራሽ ዋሻና የመዝናኛ ሥፍራ በተለምዶ ደነባ ዋሻ መስራችና ባለቤት አቶ ገመዳ ዋይሶ በ65 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
አቶ ገመዳ ዋይሶ ከ 1971 እስከ 1992 ዓ.ም ለ21 ዓመታት ዋሻውን በመቆፈር የቆዩ ሲሆን÷ ከ1992 ዓ.ም በኋላም ለህዝብ ክፍት በማድረግ አገልግሎት መስጠት እንዲችል አድርገዋል።