አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በእንግሊዝ መንግስት ልዩ መልእክተኛ ኒክ ዳየር የሚመራ የልዑካን ቡድን ጋር በወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ተወያይተዋል።
የፌደራል መንግስት ሀገራዊ ግዴታዎች በሚጥሉበት ህግጋትና የአለም አቀፍ መስፈርት በሚያስቀምጠው መሰረት ምግብ፣ መድሃኒትና ሌሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን ለተጎዱ የትግራይ ክልል ዜጎች እንዲደርሳቸው በሚደረገው ጥረት ዙርያ የሚጠበቅበትን ሀላፊነት እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።