አዲስ አበባ፣መስከረም 14 ፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ አገራት ከውጭ የሚጫንባቸውን የፖሊሲ አማራጭ ሳይሆን ከህዝባቸው ነባራዊ ሁኔታ ጋር የሚሄድ አማራጭ ሊከተሉ እንደሚገባ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ባዘጋጀው 4ኛው የቻይና አፍሪካ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሴሚናር ላይ ተጠቆመ፡፡
ዛሬ በበይነ መረብ በተደረገ ውይይት ላይ የተሳተፉት የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ÷በጥልቅ ጥናት ላይ የተመሰረተ አገር በቀል የእድገት ፖሊሲን በመተግበር ብልጽግና ለኢትዮጵያ እድገት መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል፡፡