የሀገር ውስጥ ዜና

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በሚዛን ግቢ ያስተማራቸውን ተማሪዎች በነገው ዕለት ያስመርቃል

By Feven Bishaw

September 24, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በሚዛን ግቢ ሲያስተምራቸው የቆየውን ከ1 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች በነገው ዕለት ያስመርቃል፡፡

ተመራቂዎቹ በመደበኛና በተከታታይ በማህበራዊ ሳይንስ ፣በግብርና እና በተፈጥሮ ሃብት እንዲሁም በህግ ትምህርት ክፍል ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡