የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተለያዩ ግዳጅ ላይ ተሰማርተው ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ የሚገኙ የፖሊስ አባላትን ጎበኙ

By Feven Bishaw

September 26, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ሪፈራል ሆስፒታል ተገኝተው በተለያዩ ግዳጅ ላይ ተሰማርተው ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ የሚገኙ የፖሊስ አባላትን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱ ከርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ ኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፣ በ ኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ መርዳሳ፣ የኦሮሚያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኋላፊ አቶ ፈቃዱ ተሰማና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡