የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ደመቀ መኮንን ከህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

September 26, 2021

አዲስ አበባ፤መስከረም 16፤ 2014 (ኤፍ ቢሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከህንድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብህራህማን ጃይሻንካር ጋር ተወያይተዋል።

ውይይታቸው በታላቁ የህዳሴ ግድብ እና በሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ሲሆን÷ የጋራ ጠቀሜታ ባላቸው ጉዳዮች ገንቢ ሃሳቦች ተለዋውጠዋል።