አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአገራችንን እውነት ሊጋርዱና ሊያጠለሹ የሚሞክሩ የውስጥና የውጭ ሃይሎች ሙከራ ቢያደርጉም የኢትዮጵያ እውነት እንደ ደመራው ብርሃን መድመቁ አይቀሬ ነው ሲሉ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የመስቀል ደመራን በዓል ምክንያት በማድረግ በመስቀል አደባባይ ተገኝተው ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ የመስቀል በዓል ኢትዮጵያን በዓለም ያስተዋወቃትና የቱሪዝም መስህብ በመሆኑ ትልቅ አስተዋዕኦ እያደረገ ያለ ሀገራዊ ሀብታችን ነው ብለዋል።