የሀገር ውስጥ ዜና

መስከረም 21 ለተወሰነ ሰዓት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ፖሊስ ይፋ አደረገ

By Meseret Demissu

September 30, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መስከረም 21 ቀን 2014 ዓ.ም ከፀጥታ ስራ ጋር በተያያዘ በመስቀል አደባባይ እና ዙሪያው በሚገኙ መንገዶች ለተወሰነ ሰዓት ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ ተላልፏል፡፡

ዓርብ መስከረም  21 ቀን 2014 ዓ.ም  ከጧቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ከፀጥታ ስራ ጋር በተያያዘ ለሚከናወን ተግባር በመስቀል አደባባይ እና በዙሪያው የሚገኙ መንገዶች ለተወሰነ ሰዓት ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሰረት፦

ነገ መስከረም 21 ቀን 2014 ዓ/ም ዓርብ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ለጊዜው መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆናቸውን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!