አዲስ አበባ፣መስከረም 21፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በሀገራዊ የመንግስት ምስረታና በኢሬቻ በዓል መርሃ ግብሮች ላይ የፀጥታና ደህንነት ዝግጁነት ላይ ውይይት አካሂዷል።
በውይይቱ የአገር መከላከያ፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን እና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ተቋማት ሥራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡