የሀገር ውስጥ ዜና

ኤጀንሲው ከ187 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው አጎበሮችን እያሰራጨ ነው

By Tibebu Kebede

February 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ 187 ሚሊየን 395 ሺህ ብር ዋጋ ያላቸውን 3 ነጥብ 1 ሚሊየን አጎበሮች ማሰራጨት መጀመሩን አስታወቀ።

በኤጀንሲው የመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎች ስርጭትና ተሽከርካሪ ስምሪት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አህመድ ከድር፥ ኬሞኒክስ ከተሰኘው ድርጅት ጋር በመተባበር ለሶስት ክልሎች አጎበር የማሰራጨት ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።